Updated and News
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገራት በስፋት እንዲልኩ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ወደውጭ ሀገራት በስፋት እንዲልኩ ለማድረግ አስፈላውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ፡፡
በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የኤክስፖርት ማነቆዎችና መፍትሄዎች ዙሪያ መነሻ ሰነድ ቀርቦ ከአምራች ኢንተርፕራይዞች ጋር ምክክር ተካሂዷል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጳውሎስ በርጋ እንደገለጹት ሀገራችን ካላት አቅምና #የተፈጥሮ_ጸጋ አንጻር ወደውጭ የምንልካው ምርቶች ዝቅተኛ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህን ለመቀየርና አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች #ጥራት ያላቸው ምርቶችን በማምረት ወደውጭ ሀገራት በስፋት እንዲልኩ ተቋማቸው አስፈላጊውንና ተጨባጭ ድጋፍ ለማድረግ በአዲስ መልኩ መዋቀሩንና ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በበኩላቸው #ኤክስፖርት ላይ የተሰማሩ አምራች ኢንተርፕራይዞች የሚያጋጥማቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታት ከሚመለከታቸው አስፈጻሚና ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርበው እንደሚሰሩና የኤክስፖርት ድርሻን ማሳደግ የተቋማቸው ዋነኛ ስራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ‹‹#የአምራች_ኢንተርፕራይዞች_አምባሳደር›› ሆኖ መስራቱን ይቀጥላል ያሉት አቶ አብዱልፈታ በዘርፉ የተሰማሩ አምራች ኢንተርፕራይዞች የሚያጋጥማቸውን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች #ኤክስፖርት_ማህበር መመስረት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡
በመድረኩ የተሳተፉ አምራች ኢንተርፕራይዞች በበኩላቸው ተመሳሳይ መድረኮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበው ከገበያ መረጃና መዳረሻ፣ ከውጭ ምንዛሬ፣ ከትራንስፖርትና ከብቃት የምስክር ወረቀት ጋር በተያያዘ የሚያጋጥማቸው ተግዳሮቶች እንዲፈቱላቸው ጠይቀዋል፡፡
በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች 6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያወጡ ምርቶችን ወደውጭ ሀገራት መላካቸው በውይይት መድረኩ ተገልጿል፡፡
-
“የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በዘላቂና አስተማማኝ መሠረት ላይ የማቆም አቅም ያለው እንደመሆኑ የድጋፍ ማዕከላችን ሊሆን ይገባል”
-
አምራች ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ እንዲሆኑ የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት በቁርጠኝነት መስራት ይገባቸዋል
-
በሽመና ስራ ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ተመረቁ
-
የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን “ሙስናን መከላከል በተግባር” በሚል መሪ ቃል አከበሩ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገራት በስፋት እንዲልኩ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ
-
‹‹በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው!››
-
#አንያ_የእንጨትና_ብረታብረት_ማህበር በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ የሚገኝና በእንጨትና ብረታ ብረት ውጤቶች ለይ በመሰማራት ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረና ለበርካታ ኢንተርፕራይዞች እገዛ የሚያደርግ ማህበር ነው፡፡
-
የክልልና የባለድርሻ ተቋማት አመራሮች የተካተቱበት የልኡካን ቡድን በጣሊያን ሃገር የተለያዩ ከተሞች የሚገኙና በቆዳና ተያያዥ ምርቶች ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን በመጎብኘት ላይ ናቸዉ።
-
“የአንዳችን ድክመት የሁላችንንም ክፍተት እንደሚያሳየው ሁሉ፤ የአንዳችን ጥንካሬ የሁላችን የሆነን ስኬት ያመጣል” አቶ አሸናፊ መለሠ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር EED/ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እያካሄዳቸው ባሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ውስጥ ሠራተኞች በተቋማዊ ገፅታ ግንባታው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጠየቀ፡፡ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የተቋሙ አጠቃላይ ሠራተኞች መድረክ “በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴ የሠራተኞች ሚና” በሚል ርዕስ ሠነድ ያቀረቡት የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ መለሠ እንዳብራሩት የአንድ ተቋም ምስል የተቋሙ ሠራተኞች ተቋሙን ከሚገነዘቡበትና ከሚገልፁበት መንገድ የሚመነጭ ነው፡፡ የተቋሙ ተደራሽነትም ሠራተኞች መረጃዎችን ባሠራጩበት መንገድ፣ ባሠራጩበት ልክና ይህንንም ባጎሉበት ልክ የሚመዘን ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ ሠራተኞች የሚያከናውኗቸውን ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ይህንኑ ታሳቢ ባደረገ አግባብ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ተቋሙ እንደሐገር ያለው ትልቁ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ተልዕኮ ፈፃሚ እንደመሆኑ ሠራተኞቹም በዚያው ልክ የዘርፉ ልማት አምባሳደርና የኢንተርፕራይዞች ጠበቃ መሆን እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል፡፡ ግለሠባዊ አቅም በተቋማዊ አፈፃፀም ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ እንዳለው ያብራሩት አቶ አሸናፊ ይህንን ለማጉላትም ጠቃሚነት፣ ችግር ፈቺነትና መማርና መማማርን መርሕ ያደረገ የቡድን ስሜትን መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሠዋል፡፡
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራሮችና ሰራተኞች #በእንጦጦ ፓርክ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት እያደረገ ይገኛል፡፡
-
ተወዳዳሪና ውጤታማ አምራች ኢንተርፕራይዞችን ለመፍጠር የግብዓት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
-
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በጀት
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
-
#ጣና_ጋርመንት ሕትመትና ማስታወቂያ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በወ/ሮ ፂዮን አየለ በ2011 ዓ.ም በ100 ሺ ብር ካፒታል የተመሰረተና በአጭር ግዜ ውስጥ ውጤታማ በመሆን በስሩ 37 ሰራተኞችን ቀጥሮ እያሰራ የሚገኝ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡