Updated and News
የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን “ሙስናን መከላከል በተግባር” በሚል መሪ ቃል አከበሩ
የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን “ሙስናን መከላከል በተግባር” በሚል መሪ ቃል አከበሩ
EED ህዳር15/ 2015 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሰራተኞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ በሀገራችን ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን “ሙስናን መከላከል በተግባር” በሚል መሪ ቃለ አክብረዋል፡፡
የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደተናገሩት ሙስና ልማትን በማዳከም ኢኮኖሚ እንዲገታ፣ የሞራልና የስነ ምግባር ቀውስ እንዲባባስ፣ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲሁም በህግ የበላይነት ላይ አመኔታ እንዲያጣ የሚያደርግ ደንበር ዘለል ባህሪ ያለው ወንጀል መሆኑን አብራርተዋል፡፡
አገራችን የዚህ አደገኛ ወንጀል ተጠቂ ናት ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ይህንን ለመከላከል መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራ ቢሆንም የሙስናን አስተሳሰብም ሆነ ተግባሩን ለማስወገድ ማህበረሰቡ ከመንግስት ጎን መቆም አለበት ብለዋል፡፡
አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን ለማቋቋም በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የሙስና አመለካከትና ተግባር እንዳለ የጠቆሙት አቶ አብዱልፈታ ይህንን ለማስወገድ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በግንባር ቀደምትነት መሳተፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የአገራችንን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ ኢንተርፕራይዞች ላይ የምናደርገውን ድጋፍና ክትትል ከሙስና የጸዳ ለማድግ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳ/ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ታደሰ ደገፉ በበኩላቸው አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ማዕቀፍ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ተቋማዊ አደረጃጀትና አሰራርን ማጠናከር፣ የስነ-ምግባርና የሞራል እሴቶች ግንባታን ማሳደግና ጥናት ላይ የተመሰረተ ሙስናን መከላከል ላይ ቀጣይ ትኩረት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመከላል አገሮች በተናጥል ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ በተጨማሪ በጋራ ለመታገል የሚያስችል ዓለም ዓቀፍ ኮንቬንሽን እንዲኖር የመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በውሳኔ ቁጥር 58/422 ኮንቬንሽን እንዲጸድቅ አድርጎል፡፡ የኮንቬንሽኑ ፈራሚ አገራት በጋራ በተወሰነው መሰረት በየዓመቱ ህዳር #30 ቀን የፀረ- ሙስና ቀን በማለት ያከብራሉ፡፡
-
“የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በዘላቂና አስተማማኝ መሠረት ላይ የማቆም አቅም ያለው እንደመሆኑ የድጋፍ ማዕከላችን ሊሆን ይገባል”
-
አምራች ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ እንዲሆኑ የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት በቁርጠኝነት መስራት ይገባቸዋል
-
በሽመና ስራ ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ተመረቁ
-
የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን “ሙስናን መከላከል በተግባር” በሚል መሪ ቃል አከበሩ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገራት በስፋት እንዲልኩ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ
-
‹‹በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው!››
-
#አንያ_የእንጨትና_ብረታብረት_ማህበር በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ የሚገኝና በእንጨትና ብረታ ብረት ውጤቶች ለይ በመሰማራት ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረና ለበርካታ ኢንተርፕራይዞች እገዛ የሚያደርግ ማህበር ነው፡፡
-
የክልልና የባለድርሻ ተቋማት አመራሮች የተካተቱበት የልኡካን ቡድን በጣሊያን ሃገር የተለያዩ ከተሞች የሚገኙና በቆዳና ተያያዥ ምርቶች ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን በመጎብኘት ላይ ናቸዉ።
-
“የአንዳችን ድክመት የሁላችንንም ክፍተት እንደሚያሳየው ሁሉ፤ የአንዳችን ጥንካሬ የሁላችን የሆነን ስኬት ያመጣል” አቶ አሸናፊ መለሠ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር EED/ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እያካሄዳቸው ባሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ውስጥ ሠራተኞች በተቋማዊ ገፅታ ግንባታው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጠየቀ፡፡ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የተቋሙ አጠቃላይ ሠራተኞች መድረክ “በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴ የሠራተኞች ሚና” በሚል ርዕስ ሠነድ ያቀረቡት የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ መለሠ እንዳብራሩት የአንድ ተቋም ምስል የተቋሙ ሠራተኞች ተቋሙን ከሚገነዘቡበትና ከሚገልፁበት መንገድ የሚመነጭ ነው፡፡ የተቋሙ ተደራሽነትም ሠራተኞች መረጃዎችን ባሠራጩበት መንገድ፣ ባሠራጩበት ልክና ይህንንም ባጎሉበት ልክ የሚመዘን ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ ሠራተኞች የሚያከናውኗቸውን ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ይህንኑ ታሳቢ ባደረገ አግባብ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ተቋሙ እንደሐገር ያለው ትልቁ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ተልዕኮ ፈፃሚ እንደመሆኑ ሠራተኞቹም በዚያው ልክ የዘርፉ ልማት አምባሳደርና የኢንተርፕራይዞች ጠበቃ መሆን እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል፡፡ ግለሠባዊ አቅም በተቋማዊ አፈፃፀም ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ እንዳለው ያብራሩት አቶ አሸናፊ ይህንን ለማጉላትም ጠቃሚነት፣ ችግር ፈቺነትና መማርና መማማርን መርሕ ያደረገ የቡድን ስሜትን መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሠዋል፡፡
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራሮችና ሰራተኞች #በእንጦጦ ፓርክ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት እያደረገ ይገኛል፡፡
-
ተወዳዳሪና ውጤታማ አምራች ኢንተርፕራይዞችን ለመፍጠር የግብዓት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
-
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በጀት
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
-
#ጣና_ጋርመንት ሕትመትና ማስታወቂያ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በወ/ሮ ፂዮን አየለ በ2011 ዓ.ም በ100 ሺ ብር ካፒታል የተመሰረተና በአጭር ግዜ ውስጥ ውጤታማ በመሆን በስሩ 37 ሰራተኞችን ቀጥሮ እያሰራ የሚገኝ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡