Updated and News
‹‹በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው!››
‹‹በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው!››
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ2015 1ኛ ሩብ ዓመት #የእቅድ_አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት #በኢንዱስትሪ_ኤክስቴንሽን_አገልግሎት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ተቋማቸው በትኩረት እየሰራ ነው፡
ውጤታማ የኢንዱስትሪ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ለመስጠት #አራቱን_የድጋፍ_ማዕቀፎች ባካተተ መልኩ መሰራት እንደሚገባው የገለጹት አቶ አብዱልፈታ በአዲሱ አዋጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ለኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በመሰጠቱ ክልሎች ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ም/ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ቁጥርና የስራ እንቅስቃሴ በግልጽ ስለማይታወቅ በቀጣይ መረጃዎችን በተደራጀና #በዘመነ_መልኩ ተደራሽ ለማድረግ ተቋሙ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በክልሎች ያለው የስራ አፈጻጸም ክፍተት በማጥበብ ተቀራራቢ አፈጻጸም እንዲኖራቸው የተጀመረውን ክትትልና ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን ያሉት አቶ አብዱልፈታ በተለይም #የሊዝ_ፋይናንሲንግ አገልግሎት አፈጻጸም ከክልል ክልል ሰፊ ልዩነት ያለው በመሆኑ ይህንን መቅረፍ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
በዝግጅት ምዕራፍ የነበረውን ክፍተት በመቅረፍ በቀጣይ በተሟላ ሁኔታ የዘርፉን ስራዎች ከአስፈጻሚና ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር በመስራት ውጤታማ አምራች ኢንተርፕራይዞች ለመፍጠር በትጋት መስራት እንደሚጠይቅ ተናግረዋል፡፡
በቅርቡ በሚኒስትሮች ም/ቤት የጸደቀውን አዲሱ #የኢትዮጵያ_ኢንተርፕራይዝ_ልማት_ደንብ በሚመለከት በቅርቡ አስፈላጊውን ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እንደሚሰሩም ገልጸው፡፡
-
“የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በዘላቂና አስተማማኝ መሠረት ላይ የማቆም አቅም ያለው እንደመሆኑ የድጋፍ ማዕከላችን ሊሆን ይገባል”
-
አምራች ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ እንዲሆኑ የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት በቁርጠኝነት መስራት ይገባቸዋል
-
በሽመና ስራ ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ተመረቁ
-
የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን “ሙስናን መከላከል በተግባር” በሚል መሪ ቃል አከበሩ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገራት በስፋት እንዲልኩ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ
-
‹‹በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው!››
-
#አንያ_የእንጨትና_ብረታብረት_ማህበር በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ የሚገኝና በእንጨትና ብረታ ብረት ውጤቶች ለይ በመሰማራት ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረና ለበርካታ ኢንተርፕራይዞች እገዛ የሚያደርግ ማህበር ነው፡፡
-
የክልልና የባለድርሻ ተቋማት አመራሮች የተካተቱበት የልኡካን ቡድን በጣሊያን ሃገር የተለያዩ ከተሞች የሚገኙና በቆዳና ተያያዥ ምርቶች ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን በመጎብኘት ላይ ናቸዉ።
-
“የአንዳችን ድክመት የሁላችንንም ክፍተት እንደሚያሳየው ሁሉ፤ የአንዳችን ጥንካሬ የሁላችን የሆነን ስኬት ያመጣል” አቶ አሸናፊ መለሠ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር EED/ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እያካሄዳቸው ባሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ውስጥ ሠራተኞች በተቋማዊ ገፅታ ግንባታው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጠየቀ፡፡ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የተቋሙ አጠቃላይ ሠራተኞች መድረክ “በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴ የሠራተኞች ሚና” በሚል ርዕስ ሠነድ ያቀረቡት የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ መለሠ እንዳብራሩት የአንድ ተቋም ምስል የተቋሙ ሠራተኞች ተቋሙን ከሚገነዘቡበትና ከሚገልፁበት መንገድ የሚመነጭ ነው፡፡ የተቋሙ ተደራሽነትም ሠራተኞች መረጃዎችን ባሠራጩበት መንገድ፣ ባሠራጩበት ልክና ይህንንም ባጎሉበት ልክ የሚመዘን ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ ሠራተኞች የሚያከናውኗቸውን ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ይህንኑ ታሳቢ ባደረገ አግባብ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ተቋሙ እንደሐገር ያለው ትልቁ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ተልዕኮ ፈፃሚ እንደመሆኑ ሠራተኞቹም በዚያው ልክ የዘርፉ ልማት አምባሳደርና የኢንተርፕራይዞች ጠበቃ መሆን እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል፡፡ ግለሠባዊ አቅም በተቋማዊ አፈፃፀም ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ እንዳለው ያብራሩት አቶ አሸናፊ ይህንን ለማጉላትም ጠቃሚነት፣ ችግር ፈቺነትና መማርና መማማርን መርሕ ያደረገ የቡድን ስሜትን መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሠዋል፡፡
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራሮችና ሰራተኞች #በእንጦጦ ፓርክ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት እያደረገ ይገኛል፡፡
-
ተወዳዳሪና ውጤታማ አምራች ኢንተርፕራይዞችን ለመፍጠር የግብዓት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
-
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በጀት
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
-
#ጣና_ጋርመንት ሕትመትና ማስታወቂያ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በወ/ሮ ፂዮን አየለ በ2011 ዓ.ም በ100 ሺ ብር ካፒታል የተመሰረተና በአጭር ግዜ ውስጥ ውጤታማ በመሆን በስሩ 37 ሰራተኞችን ቀጥሮ እያሰራ የሚገኝ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡