Updated and News
“የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በዘላቂና አስተማማኝ መሠረት ላይ የማቆም አቅም ያለው እንደመሆኑ የድጋፍ ማዕከላችን ሊሆን ይገባል”
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በሐገር ዓቀፍ ደረጃ ለዘርፉ አስፈፃሚዎች ሲሰጥ የቆየውን የአስፈፃሚዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡
በማጠቃለያው ላይ በበይነመረብ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የኢንዱስሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል እንደገለፁት የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በዘላቂና አስተማማኝ መሠረት ላይ የማቆም አቅም ያለው እንደመሆኑ የዘርፉን ልማት ለመደገፍ የተሠማራን በሙሉ የድጋፍ ማዕከላችን አድርገን መንቀሳቀስ ይገባናል ብለዋል፡፡
ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም ከገነቡ ሐገሮች ጀርባ ጠንካራ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት አለ ያሉት ሚኒስትሩ ይህን ተጨባጭ ዓለማዊ ሁኔታ መሠረት በማድረግ የሐገራችንን ኢኮኖሚ ለመገንባት የአምራች ዘርፉን መደገፍ የግድ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
እንደሚኒስቴር መስሪያ ቤት የአምራች ዘርፉን ለመደገፍ የተለያዩ ፖሊሲና ስትራቴጂዎችን የማሻሻልና የማዘጋጀት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የገለፁት አቶ መላኩ ከዚሁ ጎን ለጎን ለአምራች ኢንዱስትሪው ወሳኝ የሆኑ የገበያ አመራጮችን በሐገር ውስጥ በስፋት የማፈላለግ ስራዎች በውጤታማነት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታህ የሱፍ በበኩላቸው አስፈጻሚ አካላት በዘርፉ ልማት ተጨባጭ የሆነ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲችሉ በዘርፉ ልማት ዙርያ በቂ ግንዛቤን ማስያዝ ማስፈለጉን እንደመነሻ በመያዝ ሐገራዊ ስልጠናው መዘጋጀቱን አስታውሠው በግንዛቤ ማስጨበጫው መነሻነት በላቀ መነቃቃትና የግንዛቤ አቅም አምራች ኢንተርፕራይዞችን መደገፍ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
በሐገራዊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ500 በላይ አስፈፃሚዎች የተሳተፉ ሲሆን በግንዛቤ ስልጠና መድረኩ የማምረት አቅም አጠቃቀም፣ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን፣ የካይዘንና ስራ አመራር፣ የገበያና የክላስተር ማዕከላት አስተዳደርን ጨምሮ 10 ያህል የስልጠና ርዕሠ ጉዳዮችን ያካተተ ነበር፡፡ ስጠናዎቹም በአዳማ፣ ባሕርዳርና ሐዋሳ ከተሞች ተሠጥተዋል፡፡
-
“የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በዘላቂና አስተማማኝ መሠረት ላይ የማቆም አቅም ያለው እንደመሆኑ የድጋፍ ማዕከላችን ሊሆን ይገባል”
-
አምራች ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ እንዲሆኑ የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት በቁርጠኝነት መስራት ይገባቸዋል
-
በሽመና ስራ ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ተመረቁ
-
የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን “ሙስናን መከላከል በተግባር” በሚል መሪ ቃል አከበሩ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገራት በስፋት እንዲልኩ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ
-
‹‹በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው!››
-
#አንያ_የእንጨትና_ብረታብረት_ማህበር በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ የሚገኝና በእንጨትና ብረታ ብረት ውጤቶች ለይ በመሰማራት ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረና ለበርካታ ኢንተርፕራይዞች እገዛ የሚያደርግ ማህበር ነው፡፡
-
የክልልና የባለድርሻ ተቋማት አመራሮች የተካተቱበት የልኡካን ቡድን በጣሊያን ሃገር የተለያዩ ከተሞች የሚገኙና በቆዳና ተያያዥ ምርቶች ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን በመጎብኘት ላይ ናቸዉ።
-
“የአንዳችን ድክመት የሁላችንንም ክፍተት እንደሚያሳየው ሁሉ፤ የአንዳችን ጥንካሬ የሁላችን የሆነን ስኬት ያመጣል” አቶ አሸናፊ መለሠ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር EED/ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እያካሄዳቸው ባሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ውስጥ ሠራተኞች በተቋማዊ ገፅታ ግንባታው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጠየቀ፡፡ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የተቋሙ አጠቃላይ ሠራተኞች መድረክ “በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴ የሠራተኞች ሚና” በሚል ርዕስ ሠነድ ያቀረቡት የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ መለሠ እንዳብራሩት የአንድ ተቋም ምስል የተቋሙ ሠራተኞች ተቋሙን ከሚገነዘቡበትና ከሚገልፁበት መንገድ የሚመነጭ ነው፡፡ የተቋሙ ተደራሽነትም ሠራተኞች መረጃዎችን ባሠራጩበት መንገድ፣ ባሠራጩበት ልክና ይህንንም ባጎሉበት ልክ የሚመዘን ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ ሠራተኞች የሚያከናውኗቸውን ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ይህንኑ ታሳቢ ባደረገ አግባብ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ተቋሙ እንደሐገር ያለው ትልቁ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ተልዕኮ ፈፃሚ እንደመሆኑ ሠራተኞቹም በዚያው ልክ የዘርፉ ልማት አምባሳደርና የኢንተርፕራይዞች ጠበቃ መሆን እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል፡፡ ግለሠባዊ አቅም በተቋማዊ አፈፃፀም ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ እንዳለው ያብራሩት አቶ አሸናፊ ይህንን ለማጉላትም ጠቃሚነት፣ ችግር ፈቺነትና መማርና መማማርን መርሕ ያደረገ የቡድን ስሜትን መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሠዋል፡፡
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራሮችና ሰራተኞች #በእንጦጦ ፓርክ የችግኝ ተከላ አከናወኑ
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት እያደረገ ይገኛል፡፡
-
ተወዳዳሪና ውጤታማ አምራች ኢንተርፕራይዞችን ለመፍጠር የግብዓት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
-
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በጀት
-
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
-
#ጣና_ጋርመንት ሕትመትና ማስታወቂያ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በወ/ሮ ፂዮን አየለ በ2011 ዓ.ም በ100 ሺ ብር ካፒታል የተመሰረተና በአጭር ግዜ ውስጥ ውጤታማ በመሆን በስሩ 37 ሰራተኞችን ቀጥሮ እያሰራ የሚገኝ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡